የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዩንቨርስቲ ጋር በመተባበር ለእጩ ምልምል የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች የወታደራዊና የንድፈ ሀሳብ ስልጠና መስጠት ጀመረ

You are currently viewing የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዩንቨርስቲ ጋር በመተባበር ለእጩ ምልምል የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች የወታደራዊና የንድፈ ሀሳብ ስልጠና መስጠት ጀመረ

AMN – ሚያዝያ 02/2017

በይርጋለም አፖስቶ ካምፖስ በስድስተኛ ዙር ከ2000 በላይ ፓራ ሚልተሪ ኦፊሰሮችን ለማሰልጠን የሚያስችል የማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ ተከናውኗል ።

በመርሀ ግብሩ የተገኙት የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊ ሊዲያ ግርማ በአዲስ አበባ ከተማ የሚከናወኑትን የደንብ ማስከበር ተግባራት በብቃት በመወጣት ለነዋሪዎች ምቹ የሚሆንና የደንብ ጥሰቶችን በመከላከልና እርምጃ በመውሰድ በርካታ ለውጥ መመዝገቡን ተናግረዋል።

ስልጠናው የደንብ ማስከበር ስራውን የበለጠ ለማዘመን ያግዛልም ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሸነር ጀነራል መስፍን አበበ የደንብ አስከባሪዎችን አቅም መገንባት ወንጀልን ለመከላከል ጥቅሙ ሰፊ በመሆኑ ተቋማቸው የድርሻውን ይወጣል ብለዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በይርጋለም ከ2000 በላይ ለሚሆኑ ምልምሎች የሚሰጠው ስለጠና የደንብ ማስከበሩን ስራ ስኬታማ ለማድረግ ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።

ፍቃዱ ምስጋናው

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review