AMN – ጥር 22/2017 ዓ.ም
የአገልግሎት አሰጣጥን የሚያዘምኑ ሰዉ ተኮር እንዲሁም ትናንትን ከዛሬ ጋር ያሰናሰሉ የመዲናዋ የልማት ስራዎች ቃል በተግባር የተገለጠባቸዉ ናቸው ሲሉ ከመላ ሀገሪቱ የመጡ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች፤ ባለሀብቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦች ተናገሩ፡፡
የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ተጋባዥ እንግዶች ባለሀብቶች እና ታዋቂ ግለሰቦች በአዲስ አበባ ተሞክሮ የሚቀመርባቸዉን አገልግሎት ሰጭ ተቋማት እና የሰዉ ተኮር የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነዉ፡፡
የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የዘመነ ቴክኖሎጂ እና የተቀላጠፈ አገሎግሎት አሰጣጥ እና የጉለሌ የተቀናጀ የልማት መንደር የጉብኝቱ አካል ናቸዉ፡፡
በተመስገን ይመር