የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ገበያ እና የሩዋንዳው ስቶክ ኤክስቼንጅ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ

You are currently viewing የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ገበያ እና የሩዋንዳው ስቶክ ኤክስቼንጅ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ

AMN – የካቲት 9/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ገበያ እና የሩዋንዳው ስቶክ ኤክስቼንጅ አህጉራዊ የፋይናንስ ውህደትን ለማሳደግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ገበያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጥላሁን እስማዔል (ዶ/ር) እና የሩዋንዳ ስቶክ ኤክስቸንጅ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፒየር ሴሌስቲን ራባቡኩምባ ተፈራርመዋል፡፡

ስምምነቱ ትብብርን ለማጎልበት፣ እውቀትን ለመለዋወጥ እና አህጉራዊ የፋይናንስ ውህደትን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ከኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ገበያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review