የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤር ባስ A350-1000 አውሮፕላንን ተረከበ

AMN – ጥቅምት 26/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን በፈረንሳይ ቱሉዝ በተካሄደ ስነስርዓት ከኤርባስ ኩባንያ ተረክቧል።

በርክክብ ስነስርዐቱ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቦርድ ሰብሳቢ ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና የኤርባስ ኩባንያ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተረከበው ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን ዛሬ አዲስ አበባ እንደሚገባም ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review