የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሄራዊ ቡድን ወደ ቀጣይ ዙር ሳያልፍ ቀረ

You are currently viewing የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሄራዊ ቡድን ወደ ቀጣይ ዙር ሳያልፍ ቀረ

AMN – መጋቢት 6/2017 ዓ.ም

የ2026 የሴቶች ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ ዙር የመልስ ጨዋታውን ከካሜሩን አቻው ጋር ያደረገው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን 1 ለ 0 ተሸንፏል።

የካሜሩንን የማሸነፊያ ብቸኛ ግብ ታዛኑ አንጌ በ12ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፋለች።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በጨዋታው ከካሜሩን የተሻለ እንቅስቃሴ በማሳየት ብልጫ ቢወስድም ያገኛቸውን ዕድሎች ባለመጠቀሙ ለሽንፈት ተዳርጓል ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በደርሶ መልስ ጨዋታ በአጠቃላይ 6ለ2 በመሸነፍ ማጣሪያውን ሳያልፍ ቀርቷል።

በአዲሱ መንገሻ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review