የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት “በእሴታችን ትውልድን እንገባ” በሚል መሪ ሐሳብ 18ኛ ዙር የጥናትና ምርምር ጉባኤውን በማካሔድ ላይ ነው

You are currently viewing የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት “በእሴታችን ትውልድን እንገባ” በሚል መሪ ሐሳብ 18ኛ ዙር የጥናትና ምርምር ጉባኤውን በማካሔድ ላይ ነው

AMN-ሰኔ 5/2017 ዓ.ም

በጉባኤው በኦሮሞ ባህል ፣ ቋንቋ ፣ እሴትና አርት ላይ የተከናወኑ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሏል።

ትውልዱ እሴቱንና ባህሉን በሚገባ እንዲያውቅ በማስቻል የጋራ ትርክት ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ፤ መደላድልን ለመፍጠር የሚያስችል መድረክ መሆኑን የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ አስራት በተለይ ለ ኤ ኤም ኤን ተናግረዋል።

ባለፉት ስርአቶች ውስጥ ከአንድነት ይልቅ የሚለያዩ ነገሮች ላይ ትኩረት ተደርጎ ሲሰራ መቆየቱ በህዝቦች መካከከል አንዳንድ መገፋፈቶች እንዲከሰቱ ሆነዋል ፤ ያሉት አቶ ዝናቡ አሁን ግን ከሚለያዩን ይልቅ አንድ የሚያደርጉን እሴቶች ላይ በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት የህዝቦችን ወንድማማችነትና እህትማማችነትን ማጎልበት ይገባል ብለዋል።

መድረኩ ነገም ቀጥሎ የሚካሔድ ሲሆን አባ ገዳዎች ፣ ሐደ ሲንቄዎች ፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ፣ ሙሁራን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በሔኖክ ዘነበና ሰላማዊት ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review