በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙ የዘጠኝ ሀገራት አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤያቸውን ለፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ አቅርበዋል ።
በዛሬው ዕለት የሹመት ደብዳቤያቸውን ያቀረቡት የአውስትራሊያ ፣ ኩባ ፣አልጄሪያ ፣ ጋምቢያ ፣ ጆርጅያ ፣ ማይናማር ፣ታይላንድ፣ ቬትናም እና ቆጵሮስ አምባሳደሮች ናቸው ።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ እና ሌሎች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች መታደማቸዉን ከዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነዉ መረጃ ያሳያል፡፡