የጅቡቲ መንግስት ለኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ የትምህርት ቤት መስሪያ ቦታ አበረከተ

You are currently viewing የጅቡቲ መንግስት ለኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ የትምህርት ቤት መስሪያ ቦታ አበረከተ

AMN – መጋቢት 10/2017 ዓ.ም

የጅቡቲ መንግስት በሀገሪቷ ለሚገነባው የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት መስሪያ የአራት ሄክታር መሬት በስጦታ አበርክቷል።

በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ በማህበራዊ የትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት ፣ የመሬት ስጦታው ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ ያላቸውን መልካም ወዳጅነት ማሳያ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

በመስሪያ ቦታው ላይ በቅድሚያ የመዋለ−ህጻናት ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት የገቢ ማሰባሰብ እና በስራ ሂደቱ ላይ ከኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር ውይይት እየተደረገ እንደሚገኝም አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ ጠቁመዋል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review