ዶናልድ ትራምፕና ዘለንስኪ በሮም የሰከነ ዉይይት ማድረጋቸዉ ተነገረ

You are currently viewing ዶናልድ ትራምፕና ዘለንስኪ በሮም የሰከነ ዉይይት ማድረጋቸዉ ተነገረ

AMN – ሚያዝያ 18/2017

የአሜሪካዉ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና ዩክሬኑ አቻቸዉ ቮሎድሚር ዘለንስኪ በሮማዉ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀጳጳስ ብፁዕ ወቅዱስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቼስኮስ የሰንብት መርሃ ግብር ላይ ተገናኝተዋል፡፡

ሁለቱ መሪዎች ስኬታማ ነዉ የተባለለትን ውይይት ማድረጋቸዉን የነጩ ቤተ መንግስት ባለስልጣናት ተናግረዋል፡፡

መሪዎቹ ለ15 ደቂቃ ያህል የተወያዩባቸዉ አበይት ጉዳዮች ወደፊት የሚገለጹ መሆናቸዉን ነዉ የዋይት ሀውስ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሯ ስቲቨን ቼንግ የገለጹት፡፡

ዶናልድ ትራምፕና ዘለንስኪ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦቫል ኦፊስ የተገናኙ ሲሆን ዉይይታቸዉም ከፍተኛ ዉጥረት የታየበት ነበር፡፡

ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቼስኮስ የሰንብት መርሃ ግብር ጎን ለጎን ያካሄዱት ሁለተኛዉ ዉይይት ግን የሰከነ እንደነበር አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

ዶናልድ ትራምፕ እና ቮሎድሚር ዘለንስኪ የዩክሬንና ሩሲያን ግጭት ለማስቆም ጥረቶች እየተደረጉ ባለበት ወቅት ነዉ ሁለተኛዉን ዉይይታቸዉን ያካሄዱት፡፡

በወንድማገኝ አሰፋ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review