ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር የኮሪደር ልማት ስራ አስጀመሩ

You are currently viewing ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር የኮሪደር ልማት ስራ አስጀመሩ

AMN ግንቦት 26/2017

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባሰፈሩት መልእክት በከተማ የተጀመሩ የክረምት በጎ ፍቃድ ልማት ስራዎች ከገጠሩ ክፍል ጋር የማስተሳሰር አካል በሆነው የገጠር የኮሪደር ልማት ስራ እያስጀመርን ነው ብለዋል፡፡

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ ዱባንቾ ቀበሌ በገጠር ኮሪደር ሞዴል የአርሶ አደሮች መኖሪያ መንደር የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

እነዚህ ማሳያ መንደሮች መገንባታቸው አርሶ አደሩ የግብርና ስራ እያከናወነ የተሻለ ሕይወት እንዲኖር የሚያስችሉ ናቸው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review