ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባሰፈሩት መልእክት ዛሬ ከመላው ኢትዮጵያ ከተወጣጡ የንግዱ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር በዞን፣ በክልል እና ከተሞች ደረጃ ከተካሄዱ ውይይቶች የቀጠለ ውይይት ዛሬ በፌዴራል ደረጃ አካሂደናል ብለዋል፡፡
ይኽ መድረክ በየደረጃው የተሰበሰቡ የንግዱ ዘርፍ ጉዳዮች እና ሃሳቦች በሀገር አቀፍ እቅዶች እና የልማት ግቦች ዝግጅት ግብዓት ይሆኑ ዘንድ ለማካተት የተዘጋጀም ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡