በምስራቅ ሐረርጌ በተከናወነ የተፋሰስ ልማት አካባቢው ወደ ቀደመ ተፈጥሮው እንደተመለሰ ተገለጸ

You are currently viewing በምስራቅ ሐረርጌ በተከናወነ የተፋሰስ ልማት አካባቢው ወደ ቀደመ ተፈጥሮው እንደተመለሰ ተገለጸ

AMN – መጋቢት 27/2017

በምስራቅ ሐረርጌ በደኖ ወረዳ ባለፉት አመታት በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች አካባቢው ወደ ቀደመ የተፈጥሮ ሀብቱ እንዲመለስ እየረዳ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በወረዳው በተከናወነው በዚህ የልማት ስራ ተራሮች አረንጓዴ እየለበሱ፣ምንጮችም እየተመለሱ መሆኑ ተመላክቷል።

በምስራቅ ሀረርጌ ዞን የበደኖ ወረዳ አስታዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ዪዬ በተፋሰስ ስራዉ በለሙ አካባቢዎች ላይ የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውን ጠቅሰው፣ ከዚህ ውስጥ 40 በመቶ ያህሉ ለምግብነት የሚውሉ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

የተፋሰስ ስራው በማህበረሰቡ ተነሳሽነት በከፍተኛ ትጋት የተከናወነ መሆኑ አበረታች ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉንም አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

የተፋሰስ ስራውን ተከትሎ ለአካባቢው ወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር የማስተሳሰር ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ተመላክቷል።

የወረዳው ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ የልማት ስራው ከተጀመረ ወዲህ ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጸው፣ አሁንም ቀሪ አካባቢዎችን ለማልማት ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በሀብታሙ ሙለታ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review