ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ለዘመናት የኅብረ ብሔራዊነት መናኸሪያ በሆነችው በአባ ጅፋር ሀገር፣ በንግድ፣ በባህል፣ በሃይማኖትና በትምህርት ኢትዮጵያውያን ከአራቱም ማዕዘን ሲገናኙባት የኖረች ከተማ ጅማ ገብተናል ሲሉ በይፋዊ ማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ገልጸዋል፡፡
በታሪካዊቷ ከተማችን ለስድስተኛ ጊዜ የሚካሄደውን ሀገር አቀፍ የመላው ኢትዮጵያ ጨዋታዎችን እናስጀምራለንም ብለዋል።
ጅማ ከተማ ስንደርስ ደማቅ አቀባበል ላደረጉልን የፌደራል አመራሮች፣ የኦሮሚያ ክልል አመራሮች እና የጅማና አካባቢው ነዋሪዎች ሁሉ የከበረ ምስጋናም አቅርበዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡