AMN – የካቲት 4/2017 ዓ.ም
በድሬዳዋ ከተማ 8.54 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በአምስት የተለያዩ ቦታዎች በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡
እነዚህ ቦታዎች የፍሳሽ ማስወገጃ ሥራዎችን፣ የእግረኛ መንገዶችን ግንባታ፣ የብስክሌት መሥመሮችን፣ የአረንጓዴ ልማት ፕሮጀክቶችን፣ የመኪና ማቆሚያ ቦታዎችን እና የስፖርት አካዳሚ ግንባታን እንደሚያካትቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በኮሪደር ልማት ተከታታይ የምሰል አቅርቦቱ የመጨረሻው የድሬደዋ ከተማ መሆኑም ተመልክቷል።