ቻይና ዜጎቿን እስክታወጣ ድረስም በኢራን እና እስራኤል የሚገኙ ዜጎቿ እና ተቋማቶቿ ደህንነት እንዲጠበቅ ለሀገራቱ ጥሪ አቅርባለች፡፡
በአሁኑ ሰዓትም የቻይና ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት፣ ኤምባሲዎች እና ቆንፅላዎች አፋጣኝ ዝግጅት በማድረግ ላይ እንደሚገኙ የሲጂ ቲ ኤን ዘገባ ያመለክታል፡፡
በርግጥ ጦርነቱን በመስጋት ቀድመው ወደ አጎራባች ሀገራት የሸሹ ቻይናዊያንም እንዳሉ ተገልጿል፡፡
5ኛ ቀኑን የያዘው የኢራን እስራኤል ግጭት ተባብሶ ከመቀጠል ውጭ እስከአሁን ድረስ በግጭቱ ዙሪያ የተሰማ የመፍትሔ ሀሳብ የለም፡፡
በማሬ ቃጦ