AMN – ጥር 9/2017 ዓ.ም
አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ እና የፓርላማ ወዳጅነት ቡድን በኢራን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ በመሐመድ ጋሊባፍ ከተመራው የፓርላማ ልዑካን ቡድን ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ፤ ሁለቱ ሀገራት የረጅም ጊዜ ወዳጅነት ያላቸው መሆኑን ጠቅሰው የዛሬው የወዳጅነት ግንኙነትም ይህንን ማሳያና ግንኙነቱን ይበልጥ ለማጠናከር የሚረዳ መሆኑን ገልፀዋል።
በሁለቱ ወዳጅ ሀገራት ፓርላሜንታዊ ዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መካሄዱን የምክር ቤቱ መረጃ ያሳያል፡፡