የቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት አራት የአይነ-ስውራን አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት የሚያስችል የድጋፍ ስምምነት ተፈራረመ

You are currently viewing የቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት አራት የአይነ-ስውራን አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት የሚያስችል የድጋፍ ስምምነት ተፈራረመ

AMN- የካቲት 7/2017 ዓ.ም

የቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት በተለያዩ የክልል ከተሞች አራት የአይነ-ስውራን አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት የሚያስችል የድጋፍ ስምምነት ከተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች የካሊፍ ቢን ዛይድ አል-ናሃያን ፋውንዴሽን ጋር ተፈራርሟል፡፡

ስምምነቱን ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸውና እና የፋውንዴሽኑ ዳይሬክተር ጀነራል ሙሃመድ ሃጂ አልከሆሪ ተፈራርመዋል፡፡

የካሊፋ ቢን ዛይድ አል-ናሃያን ፋውንዴሽን በቅርቡ በአዲስ አበባ ከተማ ተመርቆ ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ተወጣጥተው የመጡ አይነስውራን ተማሪዎችን በማስተማር ላይ የሚገኘውን ብርሀን የአይነ-ስውራን 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤት በመገንባት ድጋፍ ማድረጉን ፅህፈት ቤቱ በመረጃው አስታውሷል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review