የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እስኪጠናቀቅ ድረስ ህብረተሰቡ ድጋፉን አጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል – ዶክተር ሂሩት ካሳው

You are currently viewing የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እስኪጠናቀቅ ድረስ ህብረተሰቡ ድጋፉን አጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል – ዶክተር ሂሩት ካሳው

AMN – መጋቢት 4/2017 ዓ.ም

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እስኪጠናቀቅ ድረስ ህብረተሰቡ ድጋፉን በቋሚነት አጠናክሮ መደገፍ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ባህል ኪነ ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ሂሩት ካሳው አሳሰቡ፡፡

‎የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት፣ የግድቡ ግንባታ የመሠረተ ድንጋይ የተጣለበትን 14ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ የገቢ ማሰባሰቢያ የንቅናቄ የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው።

‎በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ባህል ኪነ ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ሂሩት ካሳው፣ ግድቡ እየተጠናቀቀ መሆኑን አመላክተው፣ ኢትዮጵያዊያን ግድቡ እስኪጠናቀቅ ድረስ በቋሚነት መደገፍ ይገባል ብለዋል።

‎የአዲስ አበባ ከተማ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ምስክር ነጋሽ በበኩላቸው፣ ለግንባታው እስካሁን የወጣው ወጪ 240 ቢሊየን ብር ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ ከህብረተሰቡ ተሳትፎ የተገኘው 20.2 ቢሊየን ብር ያህል መሆኑን ገልጸዋል፡፡

‎በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እስካሁን ከሕብረተሰቡ እና ከልዩ ልዩ ተቋማት የተደረገው ድጋፍም 5.8 ቢሊየን ብር መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

‎ቀሪ የፕሮጀክቱ ተግባራት እስኪጠናቀቁ ድረስ ዛሬም እንደ ትላንቱ ህብረተሰቡ፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተሳትፎ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለጹት ዶ/ር ምስክር፣ ሌሎች ልዩ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞች እንደሚካሄዱም ገልጸዋል፡፡‎

‎የገቢ ማሰባሰቢያ ንቅናቄው ከመጋቢት 01 እስከ መጋቢት 30/2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚካሄድም ተመላክቷል፡፡

በሄለን ጀንበሬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review