የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በ10ኛ መደበኛ ስብሰባው በ3 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

You are currently viewing የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በ10ኛ መደበኛ ስብሰባው በ3 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በ10ኛ መደበኛ ስብሰባው በ3 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

AMN-ሚያዚያ 09/2017 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 4ተኛ አመት 10ኛ መደበኛ ስብሰባውን በ3 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

በዚህም መሰረት፤-

1ኛ. ተቋርጦ የነበረዉ የመኖርያ ቤት ህብረት ሥራ ማህበራት አገልግሎትን ለማስቀጠል ተጠንቶ የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ላይ የመልካም አስተዳደር ጥያቄን ሊፈታ በሚችል አግባብ የውሳኔ ሀሳብ አሳልፏል።

2ኛ. የብርሃን አይሰውራን፣ የመነን እና የገላን ቦርዲንግ ት/ቤቶች ካላቸው ልዩ ስምሪት፣ የጥራት ደረጃ እና ከሚያንቀሳቅሱት ሀብትና ንብረት አስተዳደር አንፃር ህጋዊ ሰውነት ኖሯቸው እንዲተዳደሩ እና ተጠሪነታቸው በቀጥታ ለከተማዉ ትምህርት ቢሮ እንዲሆን የቀረበዉን ደንብ መርምሮ አጽድቋል::

3ኛ. ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው ፕሮጀክቶች የቀረበ የመሬት ማስፋፊያ ጥያቄዎች ላይ ተወያይቶ ተገቢነት ያለዉ መሆኑን በማረጋገጥ ማጽደቁን የከንቲባ ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል::

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review