የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ እና አመራር አባላት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎበኙ

You are currently viewing የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ እና አመራር አባላት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎበኙ

AMN – የካቲት 13/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አመራር አባላት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸው የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቪርስቲ፣ የአውሮፕላን ጥገና ክፍል፣ የኢትዮጵያ ካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት እና የምስለ በረራ ክፍልን የስራ እንቅስቃሴዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው እና ከአየር መንገዱ የአመራር አባላት ጋር በአየር መንገዱ አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸውን ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር ከሚተዳደሩ የመንግስት የልማት ድርጅቶች አንዱ ነው።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review