የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ከደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

You are currently viewing የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ከደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

AMN- ጥር 19 /2017 ዓ.ም

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኢኖንሴባ ሎሲን በዛሬው ዕለት በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

በውይይታቸውም በሁለትዮሽና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን የሁለቱን ሀገራት የቆየና ታሪካዊ ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባ አንስተዋል፡፡

ዶ/ር ጌዲዮን፣ ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ ጠንካራ የሁለትዮሽ ግንኙነት ያላቸው ሃገራት መሆናቸውን ጠቅሰው ፤ አፍሪካ ኀብረትን ጨምሮ በበርካታ ባለብዙ መድረኮች ላይም በትብብር እንደሚሰሩ ገልፀዋል ።

የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኢኖንሴባ ሎሲ በበኩላቸው፣ ግንኙነቱን ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሠሩ ገልፀው ፤ ከሁለትዮሽ ግንኙነት ባሻገር በአፍሪካ ህብረት፣ በብሪክስ ማዕቀፍ እንዲሁም በሌሎች ዓለም ዓቀፍ መድረኮች የጋራ ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል ።

አምባሳደሯ በመጭው ወር ለሚካሄደው ለ38ተኛ የአፍሪካ ኀብረት የመሪዎች ጉባኤ ስኬትም በትብብር እንደሚሰሩ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review