AMN – የካቲት 4/2017 ዓ.ም
የታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች በኮሪደር ልማት በለሙና የእንግዶች መተላለፊያ በሆኑ መንገዶች ላይ ለአጭር ደቂቃም ሆነ ለሰዓት በመንገድ ዳር ማቆም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡
ከዛሬ ከንጋቱ 12:00 ጀምሮ እስከ የካቲት 09/2017 ዓ.ም ማታ 12:00 ድረስ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ በኤሌክትሮኒክ ታክሲ ስርዓት(ኤታስ) አገልግሎት የሚሰጡ፣ የሜትር ታክሲ፣ የላዳ፣ የታክሲ እና መሰል ተሽከርካሪዎች ክልከላው የሚመለከታቸው መሆኑን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ለትራንስፖርት ጉዳዮች መረጃና ጥቆማ 9417 ነፃ የጥሪ መስመር መጠቀም እንደሚቻልም ቢሮው አመልክቷል፡፡