‎‎”ስለኢትዮጵያ” የፎቶግራፍ ዓውደርዕይና የፓናል ውይይት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው

You are currently viewing ‎‎”ስለኢትዮጵያ” የፎቶግራፍ ዓውደርዕይና የፓናል ውይይት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው

AMN-መጋቢት 1/2017 ዓ.ም

የኢትየጵያ ፕሬስ ድርጅት ያዘጋጀው ሁለተኛ ምዕራፍ ሶስተኛ ዙር “ስለኢትዮጵያ” የፎቶግራፍ ዓውደ-ርዕይ እና የፓናል ውይይት በአዲስ አበባ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት እየተካሄደ ነው።

‎የሁለተኛው ምዕራፍ ሶስተኛው ዙር “ክህሎት ስለኢትዮጵያ” መርሀ-ግብር “ኢትዮጵያ እያሸነፈች ትሻገራለች” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል።

‎በመርሀ-ግብሩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ዳንኤል ተሬሳ፣ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፀዳለ ተክሉ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

‎ሁለተኛው ምዕራፍ የመጀመሪያው ዙር “ስለኢትዮጵያ” መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡታጅራ ከተማ ሁለተኛው ዙር ደግሞ በሐረር ከተማ መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 17 መድረኮች ተዘጋጅተው ስለኢትዮጵያ እንደተመከረበት ተመላክቷል።

በሄለን ጀምበሬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review