AMN – መጋቢት 4/2017 ዓ.ም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለአንጎላ ፕሬዚዳንት ጆኣኦ ማኑኤል ጎንካልቬስ ሎሬንቾን የእንኳን ደህና መጡ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ የአንጎላ ፕሬዚዳንት ጆኣኦ ማኑኤል ጎንካልቬስ ሎሬንቾን ወደ ኢትዮዽያ እንኳን ደህና መጡ ብለዋል።
በውይይታቸውም የሁለትዮሽ ጉዳዮችን ለመዳሰስ እንዲሁም ፕሬዚደንቱ በአዲሱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርነታቸው ቁልፍ አህጉራዊ እና ባለብዙወገን ጉዳዮችን ለመመልከት እንደቻሉም ገልጸዋል።