የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሀገሪቱን ፖሊስ ለማዘመን በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ነው-ኮሚሸነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል

You are currently viewing የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሀገሪቱን ፖሊስ ለማዘመን በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ነው-ኮሚሸነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል

AMN-መጋቢት 13/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሸነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የመሠረታዊ ፖሊስ ስልጠና ማዕከል ግንባታ ማስጀመሪያ የመሠረት ድንጋይ በአዋሽ ሰባት ከተማ አስቀምጠዋል።

ኮሚሸነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በሥነ-ስርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የትምህርት እና ስልጠና ማዕከላትን በመገንባት የኢትዮጵያን ፖሊስ ለማዘመን በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ የመሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ስርዓትም የዚሁ ማሳያ አንዱ አካል ነው ብለዋል ።

የሚገነባው የስልጠና ማዕከል በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ብቻ ሳይሆን ለሀገሪቱ የፖሊስ ተቋማትም የፖሊስ ስልጠና መስጠት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በአዋሽ ሰባት ማሰልጠኛ ማዕከል ስልጠና እየተከታተሉ የሚገኙ የመሠረታዊ ፖሊስ ስልጣኞችንም መጎብኘታቸውን ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review