1446ኛዉ የሹዋሊድ በዓልን ምክንያት በማድረግ የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው።

You are currently viewing 1446ኛዉ የሹዋሊድ በዓልን ምክንያት በማድረግ የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው።

AMN – መጋቢት 27/2017

በፓናል ዉይይቱ ላይ የተገኙት የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪ የሹዋሊድ በዓል በአለም ቅርስነት መመዝገቡ የቱሪዝም ሴክተሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚረዳ ነው ብለዋል።

የዘንድሮዉን የሹዋሊድ በዓል ስናከብር የለውጡን ሰባተኛ ዓመት እያሰብን የምናከብረው ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳደሩ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሁሉም ዘርፎች በርካታ ለዉጦች መገኘታቸውን ገልጸዋል።

በሐረር ከተማ ኮሪደር ልማት የተፈጠረው ንቅናቄ ከተማዋ ተሞክሮ የሚቀሰምባት እንድትሆን አስችሏልም ብለዋል።

በኮሪደር ልማት የተገኙ ውጤቶችን በሌሎች መስኮች መድገም እንደሚገባም ጠቅሰዋል።

የሐረሪ ክልል ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወለዳ አብዶሽ በበኩላቸዉ የሹዋሊድ በዓል በትውልድ ቅብብሎሽ ዛሬ ላይ የደረሰ መሆኑን ጠቅሰው ለቱሪዝም ልማት አበርክቶ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም የህዝብ ትስስርን የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል።

በዓሉ ባህላዊ ይዘቱን ጠብቆ እንዲከበር እና ለትውልድ እንዲተላለፍ እየተሰራ ነውም ብለዋል።

በሃብታሙ ሙለታ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review