የኑሮ ውድነትንና የዋጋ ንረትን ለማስተካከል በቅንጅት መስራት ይገባል – ቋሚ ኮሚቴዉ

You are currently viewing የኑሮ ውድነትንና የዋጋ ንረትን ለማስተካከል በቅንጅት መስራት ይገባል – ቋሚ ኮሚቴዉ

AMN – ሚያዝያ 04/2017

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና በተጠሪ ተቋማቱ ሲያካሄድ የቆየውን የመስክ ምልከታ አጠናቋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወ/ሮ አሻ ያህያ የኦን ላይን ንግድ ፈቃድና ምዝገባ አገልግሎት አሰጣጥ፣ የኤክስፖርት ንግድ አፈፃፀም እና የወጡ አዋጆችን ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን አመላክተዋል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኑሮ ውድነትንና የዋጋ ንረትን ከማስተካከል አኳያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል።

ከነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት አኳያ በመላ አገሪቱ የሚታየውን ቅሬታ ተከታትሎ በቅርበት መደገፍ እና በአጥፊዎች ላይ ተገቢው የእርምት ርምጃ እንዲወሰድ ማድረግ ይኖርበታል፡፡

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጐፌ (ዶ/ር) ህገ ወጥ ኬላዎች መብዛትና ተደራራቢ ቀረጥ ለኤክስፖርት ንግዱ ተግዳሮቶች መሆናቸውን ጠቁመው፤ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት በጋራ መስራት ይገባል ማለታቸዉን ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያገኘነዉ መረጃ ያሳያል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review