የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።
ዋና ፀሐፊው በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ፣ የካቶሊክ እና የዓለም ክርስቲያን ማህበረሰብ ትልቅ የሃይማኖት አባት አጥተዋል ብለዋል።
ሊቀ ጳጳሱ ለአምላክ፣ ለቤተ ክርስቲያኗ እና ለሰብዓዊነት በተሰጠ አገልግሎታቸው ሁሌም ሲታወሱ ይኖራሉ ሲሉም ገልጸዋል።