ችግኞችን በመትከል ለትውልድ ተሻጋሪ የአየር ንብረት ያላት ሀገር መፍጠር እንደሚገባ የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ

You are currently viewing ችግኞችን በመትከል ለትውልድ ተሻጋሪ የአየር ንብረት ያላት ሀገር መፍጠር እንደሚገባ የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ

AMN- ሰኔ 28/2017 ዓ.ም

ነዋሪዎቹ የዘንድሮውን የክረምት የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር የክፍለ ከተማው ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ንኢመተላህ ከበደ በተገኙበት አካሂደዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ 7ኛውን ዙር ከተማ አቀፍ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል፡፡

ይህንንም ተከትሎ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች የዘንድሮውን የክረምት ችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር አካሂደዋል።

ችግኞችን በመትከል ለትውልድ ተሻጋሪ የአየር ንብረት ያላት ሀገር መፍጠር ከአሁኑ ትውልድ ይጠበቃል ሲሉም ተሳታፌዎቹ ተናግረዋል።

በየዓመቱ በሚከናወን የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር የነዋሪው ተሳትፎ የሚያበረታታ ነው ያሉት የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ንኢመተላህ ከበደ፣ ችግኞች ከተተከሉ በኋላ መንከባከብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የክፍለ ከተማው ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘየደ ቢወጣ፣ በዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር ከ400 ሺህ በላይ የተለያዩ የጥላ እና ፍራፍሬ ችግኞች ለመትከል መታቀዱን አስታውቀዋል።

በዝናሽ ሞዲ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review