የኢራቃዊያንን ህይወት የቀጠፈው አስከፊው የእሳት አደጋ

You are currently viewing የኢራቃዊያንን ህይወት የቀጠፈው አስከፊው የእሳት አደጋ

‎ AMN   ሀምሌ 10/2017 ዓ.ም

‎‎በኢራቅ ኩት ከተማ  በገበያ ማዕከል ላይ በተከሰተ እሳት አደጋ  የ60 ሰዎች ህይወት ማለፉንና በርካቶች መጎዳታቸው ተገልጿል።

‎ከአምስት ቀናት በፊት ወደ ስራ በገባው በዚሁ ማዕከል ትናንት ምሽት የተከሰተው የእሳት አደጋ የበርካታ ዜጎችን ህይወት መቅጠፉ ነው የተነገረው። ይሁን እንጂ አሁን ላይ አደጋው በቁጥጥር ስር  ማዋሉም ተዘግቧል።

‎የፈረሳዩ የዜና ወኪል አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ፣ የህክምና ባለሙያዎችን ጠቅሶ ባወጣው ዘገባው፣ 55 ሰዎች በቀጥታ በእሳት አደጋው የሞቱ ሲሆን  ይህ ዘገባ እስከተጠናከረበት ድረስ የማቾች ቁጥር 60 ደርሷል።

‎የእሳት አደጋ ሰራተኞች ተጨማሪ አስከሬን ፍለጋ ላይ መሆናቸው ተነግሯል።

‎የአካባቢው አስተዳደር  መሃመድ አልሚያሂ አሳዛኝ አደጋ መድረሱን ገልጸው፣ የገበያ ማዕከሉ ባለቤት ላይ ምርመራና ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ተናግረዋል።

‎በኢራቅ ዜና አገልግሎት የወጣው የቪዲዮ መረጃ እንደሚያሳየው፣ የእሳት አደጋ ሰራተኞች እሳቱን ለማጥፋት በሚረባረቡበት ወቅት አደጋው ከአንዱ ወለል ወደ ሌላኛው ወለል ሲሰራጭ ተስተውሏል።

‎በሌሎች በማህበራዊ ሚዲያዎች በተዘዋወረ ምስል ደግሞ  የተወሰኑ ግለሰቦች ከህንፃው አናት እንዲሁም ከቃጠሎው መሃል ቆመው ታይተዋል።

‎አስተዳዳሪው አልሚያሂ የእሳት አደጋ ሰራተኞች የበርካቶችን ህይወት ማዳናቸውን ጠቁመዋል።

‎በቦታው እስካሁን አምቡላንሶች የከፋ ጉዳት በደረሰባቸውን 160 ኪሜ ርቀት ላይ ወደ ምትገኘው ባግዳድ ከተማ ለመውሰድ በጥድፊያ ላይ መሆናቸውም ነው የተገለጸው።

‎የአደጋ ሰራተኞች አሁንም የጠፉ ሰዎችን ፍለጋ ላይ ናቸው።

‎ለአጃንስ ፍራንስ ፕረስ ሃሳቡን ያጋራው  ዶክተር ናሲር አልቁረይሺ አምስት የቤተሰብ አባሉን በእሳት አደጋው ማጣቱን ተናግሯል።“‎

‎ ከዚያም የአየር መቆጣጠሪያው በመፈንዳቱ  ማምለጥ በማንችልበት ሁኔታ ወለሉን ሙሉ በእሳት ተያያዘ  በማለት  ሃዘናቸውን አጋርተዋል።

‎አንድ የህክምና ዶክተር በሰጠው ቃለ ምልልስ ‘ከ50 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በሞታቸውንና  በውል ያልተነሱ አስከሬኖች መኖራቸውን ገልጸዋል።

‎በሄለን ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review