ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የዛምቢያ እና የቱኒዝያ አምባሳደሮች አሰናበቱ

You are currently viewing ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የዛምቢያ እና የቱኒዝያ አምባሳደሮች አሰናበቱ

AMN ሐምሌ 16/2017

ኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የዛምቢያ አምባሳደር ሮዝ ካሸምቤ ሳካላን እና የቱኒዝያ አምባሳደር አብዱልሃሚድ ግሃሪቢን አሰናበቱ።

ፕሬዚዳንት ታዬ አምባሳደሮቹ በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ሀገራቱ ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ እንዲጎለብት ላደረጉት አስተዋፅኦ አመስግነዋል።

በሌላ በኩል ተሰናባች አምባሳደሮቹ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫነቷን በሚመጥን መልኩ ሁሉን አቀፍ እድገት እያስመዘገበች መሆኗን በቆይታቸው መገንዘባችውን ተናግረዋል።

ፕሬዚዳንት ታዬ ከሁለቱ ሀገራት አምባሳደሮች ጋር ያደረጉትን ውይይት የተከታተሉት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ዘሪሁን አበበ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ እና ቱኒዝያ ጋር ያላት ግንኙነት ዘርፈ ብዙ ነው ማለታቸዉን ተዘግቧል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review