ለቀጣዩ ትውልድ ምንዳ ለማውረስ ከተጀመሩ መርሐ ግብሮች መካከል አረንጓዴ ዐሻራ ዋናው መሆኑን ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ

You are currently viewing ለቀጣዩ ትውልድ ምንዳ ለማውረስ ከተጀመሩ መርሐ ግብሮች መካከል አረንጓዴ ዐሻራ ዋናው መሆኑን ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ

‎AMN- ሐምሌ 24/2017 ዓ .ም

‎የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) መንግስት ለቀጣዩ ትውልድ ምንዳ ለማውረስ ከጀመራቸው መካከል አረንጓዴ ዐሻራ ዋናው ነው ብለዋል።

‎የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሂደዋል፡፡

‎በመርሐ ግብሩ ላይ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ መንግስት ለቀጣዩ ትውልድ ምንዳን ለማውረስ የሚተገብራቸው መርሐ ግብሮች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው።

‎ከመርሐ ግብሮቹ መካከል አንዱና ዋናው አረንጓዴ ዐሻራ መሆኑን ገልጸዋል።

‎ዜጎች የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ጥቅምን በመገንዘብ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ እንደሆነ በመጥቀስ፤ በዛሬው የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብርም ህብረተሰቡ በከፍተኛ ደረጃ እየተሳተፈ ነው ብለዋል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review