የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለውን መስተጋብር የበለጠ ለማስተሳሰር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር መሳተፍ የዜጎች ግዴታ መሆኑን ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናገሩ ‎

You are currently viewing የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለውን መስተጋብር የበለጠ ለማስተሳሰር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር መሳተፍ የዜጎች ግዴታ መሆኑን ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናገሩ ‎

AMN- ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም

የሰው ልጅ ህይወት ከተፈጥሮ ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ ለማስተሳሰር በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር መሳተፍ የዜጎች ግዴታ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገለጹ፡፡

‎ኢትዮጵያ ለልጆቻችን እና ለልጅ ልጆቻችን የተመቸች ሀገረ እንድትሆን፣ አሁን ላይ በሀላፊነት መስራት እንደሚገባም ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል።

‎ለሚመጣው ትውልድ ትምህርትን ብቻ ሳይሆን የተመቸች ዓለምን ማውረስ ይገባል ያሉት ሚኒስትሩ፣ ይህንን ሀላፊነት ለመወጣት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ መሳተፍ የሁሉም ዜጎች ሀላፊነት ሊሆን እንደሚገባ ጠቁመዋል።

‎የምናከናውነው ተግባር ፖለቲካ አይደለም ያሉት ሚኒሰትሩ፣ በእውቀት ላይ የተመሰረተ የሰው ልጅ ህይወት ከተፈጥሮ ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ ማስተሳሰር አስፈላጊ መሆኑንም አመላክተዋል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review