መደመር በሁሉም ማህበረሰብ ውስጥ የሚገኝ ኢትዮጵያዊ እሳቤ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ

You are currently viewing መደመር በሁሉም ማህበረሰብ ውስጥ የሚገኝ ኢትዮጵያዊ እሳቤ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ

‎AMN ነሀሴ 14 /2017 ዓ.ም

‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አራተኛው “የመደመር መንግሥት” መጽሐፍ አገር በቀል መሆኑን ያስረዱ ሲሆን ፣መደመር በሁሉም ማህበረሰብ ውስጥ የሚገኝ እሳቤ መሆኑን ገልፀዋል።

‎ተመሳሳይ እሳቤዎች በሌሎች አከባቢዎች ሊኖር እንደሚችሉ ገልፀው፣ የእኛ መደመር አገር በቀል እና ኢትዮጵያ ውስጥ በስፋት የሚገኝ እሳቤ መሆኑን ተናግረዋል።

‎ ጠቅላይ ሚንስትሩ እሳቤው ኢትዮጰያ ውስጥ ሳይኖር ቀርቶ ከውጭ የገባ አይደለም ያሉ ሲሆን እሳቤውን ኢትዮጰያውያን ኖረውበታል፣ ሰርተውበታል፣ አትርፈውበታል እንደ አገርም ፀንተውበታል በማለት የመደመር እሳቤ ጥንታዊነትን አስረድተዋል።

‎መደመር በማህበረሰብ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ ለኢትዮጰያውያን አገልግሏል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እሳቤው ስርዓታዊ መልስ አልተሰጠውም እንጂ አልነበረም ማለት እንዳልሆነ ገልፀዋል። የመደመር እሳቤ በተለያየ መንገድ ሲተገበር መቆየቱንም ተናግረዋል።

‎”ድር ቢያብር አንበሳ ያስር ” አባባልን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ድር ከአንበሳ አንፃር ደካማ ቢሆንም ፣ቢያብር ግን አንበሳን ያስራል። መደመርም የዚህ ብሂል ነፀብራቅ ነው ብለዋል።

‎በእያንዳንዱ ማህበረሰብ ውስጥ መደመር በአባባሎቻችን፣ በንግግሮቻችን፣ በልምምዶቻችን፣ የኖርንበት የሰራንበት የፀናንበት እሳቤ ነው በማለት አስረድተዋል።

‎ነገር ግን ይህንን የመደመር እሳቤ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ቀመር አድርገን አላወጣነውም ሲሉ ተናግረዋል።

‎‎መደመር አገር በቀል እሳቤ የሚያደርገው ሁኔታዎችን የሚተነትንበት የመፍትሄ አማራጭ የሚያመላክበት ፤ግቡን ያስቀመጠበት፤ ሂደቱትን ያብራራበት መንገዶች በሌሎች አገሮች የማይገኝ በመሆኑ እሳቤው አገር በቀል ያስብለዋል በማለት አስረድተዋል ።

‎ በሔለን ተስፍዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review