መንግስት የትምህርት ጥራትን እና ተደራሽነትን ለማስፋት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ ገለፁ

You are currently viewing መንግስት የትምህርት ጥራትን እና ተደራሽነትን ለማስፋት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ ገለፁ

‎AMN – ነሐሴ 18/2017 ዓ.ም

‎መንግስት የትምህርት ጥራትን እና ተደራሽነትን ለማስፋት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ ገለፁ።

‎የቴክኖሊንክ ኮሌጅ በ2017 የትምህርት ዘመን በተለያዩ የሙያ መስኮች ያስተማራቸውን ከ1500 በላይ ተማሪዎችን አስመርቋል።

መርሃ ግብሩ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ ‎መንግስት የትምህርት ጥራትን እና ተደራሽነትን ለማስፋት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

‎የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጄና (ዶ/ር) በበኩላቸው ፣መንግስት ባለፉት የለወጥ አመታት የትምህርት ጥራትን እና ተደራሽነትን ለማስፋት እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

‎ተመራቂ ተማሪዎች በተመረቁበት የሙያ መስክ ማህበረስቡን በታማኝት ማገልገል እንዳለባችውም መልዕክት አስተላልፈዋል።

‎የቴክኖሊንክ ኮሌጅ ፕሬዝዳንት አቶ ደቻሳ መርጋ፤ የትምህርት ጥራት እና ተደራሽነትን ለማስፋት የሁሉንም ትብብር የሚጠይቅ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሌጁ የሀገርን እድገት የሚያስቀጥሉ ሙያተኞችን እያፈራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል፡፡

‎የትምህረት ጥራትን እና ተደራሽነትን ለማስፋት የሁሉም ትብብር እንደሚጠይቅ የተናገሩት አቶ ደቻሳ፤ ኮሌጁ የትምህረት ጥራትን ለማሻሻል በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

‎ተመራቂ ተማሪዎቹ በተመረቁበት የሙያ መስክ በታማኝነት እና በቅንንነት ሀገራቸውን ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውንም ለኤ ኤም ኤን ተናግረዋል።

‎በመሀመድኑር ዓሊ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review