የሕዳሴ ግድብ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ የድሬዳዋ ነዋሪዎች ደስታቸውን በድጋፍ ሰልፍ እየገለፁ ነው

You are currently viewing የሕዳሴ ግድብ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ የድሬዳዋ ነዋሪዎች ደስታቸውን በድጋፍ ሰልፍ እየገለፁ ነው

AMN መስከረም 12/2018

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ የድሬደዋ ነዋሪዎች ደስታቸውን በህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየገለፁ ነው።

ከማለዳ ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው የድጋፍ ሰልፍ ላይ የአስተዳደሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ነው።

የድጋፍ ሰልፈኞቹ “ግድቡ የኔ ነው፣ በህዳሴ ግድቡ የጀመርነውን ጉዞ በሌሎች ፕሮጀክቶች ላይ እንደግመዋለን፣ አባይ በአገሩ ለልማትና ለብልፅግና ውሏል፣ በህብረት ችለናል፣ ግድባችን ተጠናቋል የሚሉና ሌሎች መልዕክቶችንም በማሰማት ላይ ይገኛሉ።

በዋና ዋና ጎዳናዎች የድጋፍ ድምፃቸውን ያሰሙት ነዋሪዎች በአሁኑ ሰዓት በድሬደዋ ስታዲየም በጋራ በመሆን መልዕክታቸውን ማሰማታቸውን ቀጥለዋል።

በሰልፍ ስነስርዓቱ ላይ ከነዋሪዎች በተጨማሪ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ተሳታፊ መሆናቸዉን ተዘግቧል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review