በፍራንክፈርት ማራቶን አትሌት ቡዜ ድሪባ በሴቶች እንዲሁም አትሌት በላይ አስፋው በወንዶች አሸናፊ ሆኑ

You are currently viewing በፍራንክፈርት ማራቶን አትሌት ቡዜ ድሪባ በሴቶች እንዲሁም አትሌት በላይ አስፋው በወንዶች አሸናፊ ሆኑ

AMN-ጥቅምት 16/2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያዊቷ ቡዜ ድሪባ የፍራንክፈርት አሸናፊ ሆናለች።

የ2023 የቶሮንቶ ማራቶን አሸናፊዋ ቡዜ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 2:19:34 ሰዓት ፈጅቶባታል። የግል ምርጥ ሰዓቷ ሆኖም ተመዝግቦላታል።

በሌላ በኩል አትሌት በላይ አስፋው የ42ኛው የፍራንክፈርት ማራቶን አሸናፊ ሆኗል አትሌቱ ርቀቱን ለመጨረስ 2:06:16 ሰዓት ፈጅቶበታል።

በላይ የፍራንክፈርት ማራቶንን ያሸነፈ 6ኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሆኗል። ሌሎች ኢትዮጵያውያን ተሬሳ ቤኩማ እና ሹራ ቂጣታ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃ ይዘው ማጠናቀቅ ችለዋል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review