በመዲናዋ ውስብስብ የሆኑ ወንጀሎችን በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን የአዲስ አበባ ፓሊስ አስታወቀ Post published:May 7, 2025 Post category:መልካም አስተዳደር AMN – ሚያዝያ 29/2017 በመዲናዋ ሲያጋጥሙ የነበሩ ውስብስብ የሆኑ ወንጀሎችን በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን የአዲስ አበባ ፓሊስ አስታውቋል፡፡ በመዲናዋ በመቀናጀት በተሰሩ ስራዎች በአደባባይ የተከበሩ በዓላት እና ኮንፈረንሶች ያለምንም ችግር መከናወናቸውን የአዲስ አበባ ፓሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ተናግረዋል። ለስራ ምቹ የሆነ፣ ተወዳዳሪና ደረጃውን የሚመጥን ተቋም የመገንባት ስራ ሰላምን ከማስፈን ጎን ለጎን ስለመከናወኑም ኮሚሽነር ጌቱ አመላክተዋል፡፡ የማህበረሰቡን ሰብዓዊ መብቶች የጠበቀ ህጋዊና አስተዳደራዊ አገልግሎት የመስጠት ስራ በአዲስ አበባ ፓሊስ የተከናወነ እና እየተከናወነ ያለ ተግባር መሆኑም ተመላክቷል፡፡ ከአፍሪካ አምስት ከተሞች የአዲስ አበባ ፓሊስን በአገልግሎት አሰጣጡ ተጠቃሽ ለማድረግ በቴክኖሎጅ የታገዘ ተቋም መገንባት ላይ በትኩረት ስለመሰራቱ ተጠቅሷል። አዲስ አበባን ከወንጀልና ከፀጥታ ስጋት የፀዳች ከተማ ለማድረግ ተቋሙ፣ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ባከናወናቸው ተግባራት ላይ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች ከተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ይገኛሉ። በንጉሱ በቃሉ 0 Reviews ( 0 out of 0 ) Write a Review Submit Review You Might Also Like የአዲስ ምዕራፍ ፕሮግራም በመገናኛ ብዙኃን አዋጁ መሰረት ከስርጭት ታግዶ እንዲቆይ መወሰኑ ተገለጸ April 2, 2025 ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ የስነምግባር ጉድለት በተገኘባቸው ከ1ሺህ 800 በላይ አመራሮችና ሰራተኞች ላይ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ May 1, 2025 ሀሰተኛ የባቡር ትራንስፖርት ትኬት በማዘጋጀት ሲሸጥ የነበረ የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ሰራተኛ በቁጥጥር ስር ዋለ July 25, 2025
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ የስነምግባር ጉድለት በተገኘባቸው ከ1ሺህ 800 በላይ አመራሮችና ሰራተኞች ላይ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ May 1, 2025
ሀሰተኛ የባቡር ትራንስፖርት ትኬት በማዘጋጀት ሲሸጥ የነበረ የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ሰራተኛ በቁጥጥር ስር ዋለ July 25, 2025