AMN- ጥቅምት 1/2017 ዓ.ም
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት ዛሬ ከሰዓት በኋላ የቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር እና የቶኒ ብሌር ኢንስቲቲዩት ዋና ሊቀመንበር የሆኑትን ቶኒ ብሌርን ተቀብያለሁ ብለዋል።
መጠነ ርዕይ ባላቸው ዓለም አቀፍ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይም ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውንና ተቋማቸው በኢትዮዽያ እያደረገ ያለውን ድጋፍ በተመለከተም መነጋገራቸውን አክለዋል።