AMN-ጥር 4/2017 ዓ.ም
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀሥላሴ ከኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡
ውይይቱ በኡጋንዳ እየተደረገ ካለው የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ) ጉባኤ ጎን ለጎን ነው ፡፡
ፕሬዚዳንቱ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት ፅሁፍ፤ በውይይቱ ግብርናን ማዘመን፣ የአባይ ዉሃ በፍትሃዊነት መጠቀም እና የአፍሪካ ህብርትን ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል፡፡