AMN – መጋቢት 2/2017 ዓ.ም
አሜሪካ እና ዩክሬን በሳዑዲ ዓረቢያ የሚያደርጉት የሰላም ንግግር በሚጠበቅበት ሰዓትምሽቱን ዩክሬን የድሮን ጥቃት በሞስኮ ላይ መፈፀሟን ሩሲያ ገልፃለች፡፡
ዩክሬን ወደ ሞስኮ ከሰነዘረቻቸው ድሮኖች መካከል 73 ድሮኖችን ሩሲያ መታ መጣሏን የሞስኮው ከንቲባ ሰርጌይ ሶቢያኒን ገልፀዋል፡፡
የተፈጠረውን የፀጥታ ችግር ተከትሎም አራት በሞስኮ ከተማ የሚገኙ አየር መንገዶች በረራዎችን ሰርዘዋል፡፡
እንደ ቢቢሲ ዘገባ ማምሻውን ዩክሬን የከፈተችው ጥቃት ከእስካሁኑ የከፋ ሲሆን በጥቃቱ የሁለት ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡