ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባሰፈሩት መልዕክት የንግዱን ማህበረሰብ እና አምራች ኢንዱስትሪዎችን ባወያየንበት ወቅት በቀረቡልን ጥያቄዎች መሰረት መልስ እየሰጠን እንገኛለን ብለዋል።
አዲስ አባባ ቀን ብቻ ሳይሆን ሌሊትም የሚሰራባት ከተማ እየሆነች ነው ።
ዛሬ ለአዲስና ለማስፋፊያ አምራች ኢንዱስትሪዎች ለሚቀርቡ የመስሪያ ቦታ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በገባነው ቃል መሰረት ግልፅ መስፈርት አዉጥተን በመስፈርቱ ቅድሚያ ለሚገባቸዉ አምራቾች ኢንዱስትሪዎች ቁልፍ ርክክብ አድርገናል ::
የመስሪያ ቦታ ቁልፍ የተረከባችሁ አርዓያ የሚሆን ስራ ሰርታችሁ ምርታማነትን በመጨመር እና የስራ እድል በመፍጠር ገበያን ማረጋጋት ይጠበቅባችኋል ፡፡
ያለንን መሬትና የሰው ሃይል ተጠቅመን በእልህ ስኬታማ እንሁን ፤ አምራቾችም ትልቅ ህልም ኖሯችሁ ዉጤታማ ሥራ ከእናንተ ይጠበቃል ሲሉ ገልጸዋል።