ቀናቶችን ያስቆጠረው አውዳሚው የኢራን -እስራኤል ጦርነት በሀገራቱ መከላከያ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረሱን የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገልፀዋል::
ፕሬዚዳንቱ ሁለቱ ሃገራት ያለምንም ቅድመሁኔታ ሙሉ በሙሉ አጠቃላይ የተኩስ አቁም ስምምነትን በሰዓታት ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ መስማማታቸውን አረጋግጠዋል።
ነገር ግን በስራኤልም ሆነ ኢራን በኩል ስለተኩስ አቁም ስምምነቱ ምንም የተባለ ነገር የለም። ይልቁንም እስራኤል የአየር ድብደባዋን አለማቆሟን እና ይህም ኢራን አጸፋዊ ምላሽን እንድትሰጥ የሚጋብዝ መሆኑን ነው አልጄዚራ የዓይን እማኞቹን ጠቅሶ የዘገበው።
በወርቅነህ አቢዮ