የአዲስ አበባ ሆቴሎች አገልግሎት አሰጣጣቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር እንዲችሉ ሰልጣኞች ያላቸዉ አበርክቶ የጎላ እንደሆነ ሂሩት ካሳዉ (ዶ/ር) ተናገሩ::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል ፣ ኪነ ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ ከስራ እና ክህሎት ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን ከሁሉም ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ 1 ሺህ 900 ሰልጣኞችን አስመርቀዋል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ባህል ፣ ኪነ ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሂሩት ካሳዉ (ዶ/ር) አዲስ አበባ የተለያዩ ዲፕሎማቶች እና አምባሳደሮች መቀመጫ እንደመሆኗ በሆቴል ዘርፉ ላይ አበክሮ መስራት ይገባል ብለዋል።
በዛሬዉ ዕለት በሆቴል ማኔጅመንት ፣ በምግብ ዝግጅት ፣ በእንግዳ አቀባበል ፣ በመስተንግዶ እና በቤት አያያዝ በአጠቃላይ በአምስት ዘርፎች የሰለጠኑ ሰልጣኞች ተመርቀዋል፡፡
የአዲስ አበባ ሆቴሎች አገልግሎት አሰጣጣቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር እንዲችሉ የራሳቸውን አበርክቶ ማኖር እንደሚገባቸው ተመላክቷል፡፡
በትባረክ ኢሳያስ