በጉብኝቱ አባ ገዳዎች፣ ሀደ ሲንቄዎች፣ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች፣ ከዞን እና ከወረዳ የተውጣጡ ዳኞች እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው በአጠቃላይ ከ500 በላይ የሚሆኑ ጎብኝዎች ተሳትፈዋል።
የኦሮሚያ ኪነጥበብ ማዕከል፣ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ የኦሮሚያ ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት እና የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከተጎበኙት ፕሮጀክቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው።
በከተማዋ የተሰሩ እነዚህ ፕሮጀክቶች የኦሮሞን ባህልን እና እሴትን ለቀሪው አለም ከማስተዋወቅ ባለፈ የከተማዋን የቱሪዝም ዘርፍ የሚያበረታቱና የሚያስተዋዉቁ ስለመሆናቸው ተጠቁሟል።
በአይናለም አባይነህ