የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ስራ ለትውልድ የሚተላለፍ መልካም ተግባር መሆኑን አቶ ግርማ ሰይፉ ተናገሩ

You are currently viewing የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ስራ ለትውልድ የሚተላለፍ መልካም ተግባር መሆኑን አቶ ግርማ ሰይፉ ተናገሩ

AMN- ሰኔ 22-2017 ዓ.ም

የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ስራችን ገብቶን የምንሰራው ለትውልድ የምናስተላልፈው መልካም ተግባር ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ ተናግረዋል፡፡

ሰባተኛው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ በይፋ ተጀምሯል፡፡

በማስጀመሪያ መርሐ-ግብሩም፣ የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ ባለፉት ስድስት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ስራዎች የተገኙ ውጤቶች አጠናክሮ በማስቀጠል ዘንድሮም ለትውልድ የሚሸጋገር አሻራችንን የምናስቀምጥበት እና ራስ ወዳድ አለመሆናችንን እና ነገን አሻግረን የምናይ መሆናችንን በተግባር ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል፡፡

ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ለልጆቻችን የሚወረስ አሻራ የማስቀመጥ ዋልታና ምሰሶ ነው ሲሉም አክለዋል፡፡

የምግብ ሉዓላዊነታችንን ለማረጋገጥም በትኩረት የምንሰራበት ነው ብለዋል፡፡

ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ለወዳጅም ለጠላትም ገብቶን የምንሰራው ስራ መሆኑን የምናሳይበት ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡

በያለው ጌታነህ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review