ከተማ አስተዳደሩ በእርጅና ምክንያት በፈረሰዉ ህንፃ ምትክ ያስገነባውን ሁለገብ ህንጻ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ማስረከባቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ

You are currently viewing ከተማ አስተዳደሩ በእርጅና ምክንያት በፈረሰዉ ህንፃ ምትክ ያስገነባውን ሁለገብ ህንጻ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ማስረከባቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ

AMN- ሰኔ 23/2017

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በኮሪደር ልማት እና በእርጅና ምክንያት በፈረሰዉ ህንፃ ምትክ ያስገነባውን ሁለገብ ህንጻ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በተገኙበት የምርቃት ስነስርአት ላይ ለቤተክርስቲያኗ አስረክበናል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በይፋዊ ማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል፡፡

ሁለገብ ህንፃዉ በአራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ አካባቢ በተለምዶ መሐሙድ ሙዚቃ ቤት በመባል በሚታወቀዉ የቤተክርስቲያኗ ይዞታ ላይ የተገነባ መሆኑንም ከንቲባዋ ተናግረዋል፡፡

አክለውም በከተማ አስተዳደሩ በጀት ደረጃዉን በጠበቀ መልኩ በዛሬዉ ዕለት የተመረቀዉ ህንፃ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ የተጠናቀቀ ነዉ ብለዋል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review