ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተያዘዉን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እቅድ ለማሳካት ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ2017 ዓመተ ምህረት የእቅድ አፈፃፀም ከማቅረብ ባሻገር በፓርላማ ምድረ ግቢ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ በመትከል ሁሉም ለዚህ አመት የተያዘውን ግብ ለማሳካት መረባረብ እንደሚገባዉ ጥሪ ማቅረባቸዉን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል፡፡