የናይጄሪያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ቡሃሪ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

You are currently viewing የናይጄሪያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ቡሃሪ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

AMN-ሐምሌ 06/2017

የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ሙሀመዱ ቡሃሪ በ82 ዓመታቸው ነው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት።

ቡሃሪ ከሶስት ተከታታይ የምርጫ ወቅቶች ሽንፈት በኋላ በ2015 ድል የቀናቸው የመጀመሪያው ተፎካካሪ ፓርቲ መሪ ነበሩ።

በ2015 የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ለመሆን የበቁት ቡሃሪ በፈረንጆቹ 2019 ለ2ኛ ጊዜ ተመርጠው ሀገሪቱን በፕሬዝዳንትነት መርተዋል።

ቡሀሪ በተደጋጋሚ ጊዜ ጤናቸውን ለመታየት ወደ ለንደን ይሄዱ የነበረ ሲሆን ባለፈው ሚያዝያ ወር ላይ ግን ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ለንደን እንዳቀኑ ተሰምቷል።

በዛሬው እለትም ህክምና በሚከታተሉበት ክሊኒክ ውስጥ ህይወታቸው ማለፉን ቢቢሲ ዘግቧል።

በማሬ ቃጦ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review