የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሬጅስተራል የአንድ መስኮት አገልግሎት መስጠት ጀመረ

You are currently viewing የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሬጅስተራል የአንድ መስኮት አገልግሎት መስጠት ጀመረ

‎AMN- ሐምሌ 8/2017 ዓ.ም

‎ለተገልጋዮች በአንድ ቦታ የተለያዩ አገልግሎቶችን ማግኘት የሚያስችለው የሬጅስተራል የአንድ መስኮት አገልግሎት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት መሰጠት ተጀምሯል።

‎የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረትና የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ሌሊሴ ደሳለኝ የአንድ መስኮት አገልግሎቱን አስጀምረዋል።

የችሎት ፀሐፊ፣ የሬጅስትራል፣ የፋይል ከፋች፣ የዳታ፣ የመረጃ ዴስክ፣ የፋይናንስ ጉዳዮች እና የመልዕክት ክፍልን ጨምሮ ‎በፍርድ ቤቱ የሚሰጡ አገልግሎቶች በአንድ መስኮት ለማግኘት ያስችላል።

‎የአንድ መስኮት አገልግሎት መጀመሩ በህገ-መንግሥቱ እና በሌሎች ህጎች መሰረት ነፃና ገለልተኛ በሆነ መንገድ አገልግሎቱን ለተገልጋዮች ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችል የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ሌሊሴ ደሳለኝ ተናግረዋል።

‎የአንድ መስኮት አገልግሎቱ፣ በአንድ ቦታ የተለያዩ አገልግሎቶችን ከማስገኘቱ በተጨማሪ ፈጣንና ከዚህ በፊት በተገልጋዮች ይቀርቡ የነበሩ ቅሬታዎችን የሚቀርፍ መሆኑንም ወ/ሮ ሌሊሴ አመላክተዋል።

‎በሔለን ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review